“ምርጫው የዲሞክራሲ መገለጫ በመሆኑ፣ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የፍትህ አካላት የሕግ የበላይነትን የማስከበርና የዜጎችን መብት የማስጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው” ብለዋል አቶ ሙሉቀን ታደሰ

May 26, 2026

ወላይታ ሶዶ፣ ግንቦት 06/2018 ዓ.ም

Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ታደሰ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ “ምርጫ የዲሞክራሲ መገለጫ እንደመሆኑ፣ ይህ ሂደት በስኬት እንዲጠናቀቅ የፍትህ አካላት የሕግ የበላይነትን የማስከበርና የዜጎችን መብት የማስጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው” ብለዋል።

ምርጫ የሀገር መንግሥት ግንባታ ምሶሶ ከመሆኑ አንጻር የፍትህ ተቋማት ገለልተኝነት ወሣኝ ጉዳይ ብለዋል።

የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕረዚዳንት አቶ ምህረት ኩኬ እንዳብራሩት የምርጫ ሥነምግባር ለማስጠበቅ የፍትህ አካላት ገለልተኝነት ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል።

በምርጫ ወቅት ወንጀሎች ስከሰቱ የሰብአዊ መብት በማይጋፋ መንገድ እንዲሆን አሳስበዋል

የምርጫ ወንጀሎች በመለየት ፈጣን ፍትህ እንዲሰጥ ጊዚያዊ ችሎት መዘጋጀቱን አስረድተዋል

ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዲሆን የፍትህ ተቋማት ቁርጠኝነት ወሣኝ መሆኑን ገልጸዋል

የጸጥታ አካላት ገለልተኝነት ለምርጫው ውጤታማነት የጎላ ሚና እንደሚጫወት አስረድተዋል

ሠላማዊ ምርጫ ለማካሄድ ቅድሚያ ችግሩን በመለየት በመከላከል ላይ መሠረት በማድረግ ውጤታማነትን ለማስመዝገብ እንደሚሠራ ጠቁመዋል

የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጸጋው ስሞኦን እንደገለጹት የጸጥታ አካላት ገለልተኛ እንዲሆንና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ሥልጠናው ወሳኝ ጉዳይ መሆኑ የተገለጸው።

የምርጫ ቦርዶ አዋጅ መሠረት በማድረግ የጸጥታ አካላት ሕጉን በተከተለ መንገድ ተግበራዊ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

ፍትሕ ተቋማት ምርጫው በሕግ አግባብ እንዲያከናውኑ ሥልጠናው አቅም እንደሚፈጥር አስተያየታቸውን ገልጸዋል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ እና የወላይታ ዞን ፍትህ አካላት በጋር በመሆን ለሥር መዋቅር አካላት ማለትም ለቦዲቲ ከተማ፣ ለዳሞት ጋሌ፣ ለዳሞት ፑላሳ እና ለሻንቶ ከተማ ለተውጣጡ ዐቃቢያነ ሕጎች፣ ዳኞች፣ የፖሊስ አባላት እና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ያዘጋጁት የአቅም ግንባታ ስልጠና እና የምክክር መድረክ በቦዲቲ ከተማ በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

‎በመድረኩ 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ብቻ እንዲመራ፣ በምርጫ ሕጉ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎችንና የወንጀል ተጠያቂነትን በተመለከተ ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሯል።