የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች መረጃ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ ዙሪያ ለክልልና ለሥር መዋቅር ዓቃቢያነ ህግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል

March 8, 2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች መረጃ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ ዙሪያ ለክልልና ለሥር መዋቅር ዓቃቢያነ ህግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል።

Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!

ወላይታ ሶዶ፣ የካቲት 14/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች መረጃ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ ዙሪያ ለክልልና ለሥር መዋቅር ዓቃቢያነ ህግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።

የሥልጠና መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የፍትህ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ወንድማገኘሁ አበበ እንደተናገሩት ሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ከማድረስ ባሻገር ሥነልቡናዊም ጉዳት በማድረስ አሉታዊ ተጽእኖአቸው ከፍ ያለ ነው።

በወንጀሎቹ ዙሪያ የመረጃ አሰባሰብ እና ሪፖርት አቀራረብ ላይ የሚሰጠው ሥልጠና ወንጀሉን ለመመርመር መረጃ በመስጠት የሚያግዝ ከመሆኑም በላይ የተሻለ የፍትህ ውሳኔ ለመስጠት እንደሚያግዝ ተናግረዋል።