‎ከብልሹ አሰራርና ከአድሎ የፀዳ የፍትህ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

March 8, 2026

‎ከብልሹ አሰራርና ከአድሎ የፀዳ የፍትህ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ።

Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!

‎ላስካ፡ የካቲት 24/2018 ዓ.ም

‎የባስኬቶ ዞን ፍትህ መምሪያ 2018 ዓ.ም የመጀመሪያውን ሴክቶሪያል ጉባኤ አካሂዷል።

‎የፍትህ ተቋማት ትክክለኛና ተገቢነት ያለው ፍትህ ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዕጩ ዶክተር ሳሙኤል ደሳለኝ አስገንዝበዋል።

‎የፍትህ ሥርዓቱን ለማዛባትና ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ያሳሰቡት አስተዳዳሪው ህግና አሰራርን ያልተከተሉ አሰራሮችን በመለየት ተገቢውን እርምጃ መውሰድ ይገባል ስሉ ተናግረዋል።

‎አስተዳዳሪው አክለውም በዞኑ ጠንካራ የፍትህ ሥራዓትን ለመዘርጋት ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በተገቢው እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

‎በዞኑ ከብልሹ አሰራርና ከአድሎ የፀዳ የፍትህ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የባስኬቶ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚልክያስ ተሰማ ተናግረዋል።

‎ለህብረተሰቡ እየተሰጠ የሚገኘውን የፍትህ አገልግሎት ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሚገኝ አቶ ሚልክያስ ገልጸዋል።

‎በመድረኩ የተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ሪፖርትና የተቋሙ የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በተቋሙ ልማት ዕቅድ ሥራ ሂደት አስተባባሪ በአቶ ሳሙኤል አሽኩ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

‎ከህዝቡ በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎችን በመፍታት ፍትህን በማረጋገጥና ዘላቂ ልማት ማስፈን እንደሚገባም ተመልክቷል።

‎በመድረኩ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው መልካም ጅምሮችን ለማስቀጠልና ጉድለቶችን በማረም የተገልጋይ እርካታን ለመጨመር እንደሚሰሩም ተናግረዋል።

‎    የካቲት 24/2018 ዓ.ም

‎          ላስካ