የፍትህ ተደራሽነትን በማረጋገጥ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በላስካ ዙሪያ ወረዳ ሰፊ ሥራ እየተሰራ ይገኛል።
Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!
ላስካ፦የካቲት 25/2018 ዓ.ም(ዙሪያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)
⚖️ ⚖️ ⚖️ ⚖️ ⚖️ ⚖️ ⚖️ ⚖️ ⚖️ ⚖️
የባስኬቶ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ በአቶ ሚልክያስ ተሰማ የተመራ ልዑክ በዳብፃ ዳልቅንሳ ነፃ የሕግ ድጋፍ ማዕከል በመገኘት የአገልግሎት አሰጣጡንና ያለበትን ደረጃ የመስክ ምልከታ ተደርጓል።
መምሪያ ኃላፊው አቶ ሚልክያስ ተሰማ የፍትህ ተቋማት ዋነኛ ተልዕኮ ሕዝብን በቅንነትና በቀልጣፋ አሠራር ማገልገል ነው ስሉ ገልፀዋል።
በማዕከሉ ውስጥ የተገልጋዩን ምቾት የሚጠብቁ አሠራሮችን መዘርጋት አገልግሎቱን ለሕዝቡ ቅርብና ግልጽ ማድረግ እንዲሁም በሥራ ሂደት ላይ የሚታዩ ማነቆዎችን በፍጥነት በመፍታት ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
የላስካ ዙሪያ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አቤነዘር መሰለ ማዕከሉ የሚጠበቅበትን ሰብአዊና ሙያዊ ግዴታ በብቃት እንዲወጣ ለማድረግ ጽ/ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደማይለየው ገልፀዋል።
አክለው ህብረተሰቡ መብቱንና ግዴታውን ጠንቅቆ እንዲያውቅ የሚያስችሉ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ወንጀል የማይፈጸምባት ሞዴል ቀበሌ ለማድረግ በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ላይ የተመሠረተ የጥበቃና የክትትል ሥርዓት ለመዘርጋት ታልሞ እየተሰራ እንደሚገኝ ተጠቅሷል።
የቀበሌው አመራሮችና ነዋሪዎች የሰላምና የፍትህ ባለቤት በመሆን በቀጣይ የሚጠበቁባቸውን ሥራዎች በቁርጠኝነት ለመወጣት ኃላፊነታቸውን ልወጡ እንደሚገባ ተገልጿል።
የካቲት 25/2018ዓ.ም
ላስካ
ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች አገልግሎት











