WELCOME TO THE SOUTH ETHIOPIA REGION STATE JUSTICE BUREAU
WE STAND TOGETHER FOR LAW,JUSTICE AND EQUITY!
Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Introduction
The Southern Ethiopia Regional Government has recently established the 12th regional state of the federation, and the executive bodies of the region have been reorganized under Proclamation No. 3/2015, Article 9/22/. One of the newly established sector offices is the Justice Bureau. The Bureau has been entrusted with the tasks and organization and procedures for youth from the region to the A service that meets the needs of the previous administrative levels of families, ensures the rule of law required in the center, and meets the needs of the community, which is efficient and accessible, and meets the needs of the service user community. In order to provide and satisfy the needs of the users, it is hoped that a consistent institutional arrangement will be developed and implemented from region to woreda by exchanging experiences with other peer regions, incorporating the experiences gained, and adapting them to the actual conditions of our region.








LATEST NEWS
የይቅርታ መስፈርቱን ላሟሉ በክልሉ ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ ታራሚዎች ይቅርታ ተደረገ፡፡
(ሚያዚያ 2/2018፣ሳውላ ፣ ፍትህ ቢሮ)የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ታደሰ ይህን አስመልክተው ማብራርያ የሰጡ ሲሆን የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ፍትህ ቢሮ በክልሉ የይቅርታ አሰጣጥ ህግን መስፈርት በማድረግ በክልሉ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች በ2018 ዓ/ም በሶስተኛ ዙር ይቅርታ እንዲደረግላቸው ከማረሚያ ተቋማት በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ላይ የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል የይቅርታ ቦርድ መጋቢት 30/2018 ዓ/ም ባካሄደው ስብሰባ ተወያይቶ መስፈርቱን ላሟሉ 625 /ለስድስት መቶ ሃያ አምስት/ ታራሚዎች ይቅርታ እንዲደረግላቸው ውሳኔ አሳልፏል ብለዋል፡፡በዚሁ መሰረት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደርም የቀረበውን የቦርዱን የውሳኔ ሀሳብ ተቀብለው አፅድቀዋል፡፡
736 ታራሚች በይቅርታ እንዲለቀቁ ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን ወንድ 593፣ ሴት 32 በድምሩ 625 ታራሚዎች የይቅርታ መስፈርቱን አሟልተው በመገኘታቸው ይቅርታ የተደረገላቸው መሆኑን ገልጸው፤ ከነዚህ ውስጥ 2(ሁለቱ) የእስራት ተቀናሽ የተደረገላቸው እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡111 (አንድ መቶ አስራ አንድ) ታረሚዎች የይቅርታ መስፈርቱን አሟልተው ባለመገኘታቸው የይቅርታው ተጠቃሚ አለመሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
ይቅርታ ከማያሰጡ ምክንያቶች መካከል የተፈጸመው የወንጀል ክብደት፣ለተጎጅ /ቤተሰብ ካሳ አለመክፈል፣ከተጎጅ ቤተሰብ ጋር እርቅ አለመፈጸም የሚሉት እንደሚገኙበት ነው የተናገሩት፡፡
አያይዘውም ከማረሚያ ተቋማት ከግል ተበዳይ እና ከግል ተበዳይ ቤተሰብ ጋር ታራሚዎች ዕርቅ ፈፅመናል በማለት ያቀረቡትን ሰነድ ከክልሉ ማረሚያ ተቋም እና ከክልሉ ፍትህ ቢሮ ጋር በጋራ ማጣራት የተደረገ ስሆን የዕርቅ ሰነድ የቀረበ ቢሆንም የዕርቅ አካል ተደርገው በሰነድ ላይ ፈርመዋል የተባሉት የግል ተበዳይ ሆነ የግል ተበዳይ ቤተሰብ ጥሪ ተደርጎ ባለመቅረባቸው የተነሳ በዕርቅ ሰነድ ላይ የህጋዊነት ጥያቄ በመነሳቱ ምክንያት ውድቅ ተደርጓል፡፡
በመጨረሻም የይቅርታ ተጠቃሚዎች ወደ ህብረተሰቡ በሚቀላቀሉበት ጊዜ በልማት ስራዎች፣በማህበራዊና በልዩ ልዩ መልካም ተግባራት ላይ መሳተፍ፣መተባበር እንደሚኖርባቸው አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል ፡፡
የቢሮ ሀላፊው በስተመጨረሻ እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸው ከክርስቶስ የተማርነውን ትህትናና ይቅርታን መሠረት በማድረግ አንዳችን ለአንዳችን አቅም ሁነን በጎነትንና ፍቅርን ከፍ በማድረግ የክርስትናን ስርዓት ለዓለም በማሳየት ሠላምን መስበክ ይኖርብናል ብለዋል። ክርስቶስ ዓለምን በፍቅር እንዳሸነፈ ሁሉ እኛ ልጆቹም የፍቅርና የሠላም ተምሳሌት መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።
በስተመጨረሻም ከክርስቶስ የተማረነውን ፍቅር በመከተል ክርስትናን የሠላም ተምሳሌት በማድረግ ለዓለም እንድናሳይ እያልኩ በዓሉ የሰላምና የፍቅር እንዲሆን እመኛለሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ2018 የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ከቢሮ ማኔጅመንት አመራር ጋር ገመገመ። 21/07/2018
**************************************
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት 3ኛ ሩብ ዓመት (9 ወራት) የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን የገመገመ ሲሆን፣ በህግ የተጣለበትን ተልዕኮ በማስፈፀም አስፈላጊ ውጤቶች መመዝገቡን ገልጿል።
ቢሮው የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ የዜጎች መብት ለመጠበቅ እና የፍትህ አገልግሎትን ተደራሽና ጥራት ያለው ለማድረግ በርካታ ስራዎችን አከናውኗል። በዚህም የወንጀል ክሶችን በፍ/ቤት መመስረት፣ የሙስናና የታክስ ወንጀሎችን መከታተል፣ የህግ ግንዛቤ መፍጠር እና የህግ ረቂቆችን የማዘጋጀት ተግባራት እንደተከናወኑ ተገልጿዋል።
በታክስ ማጭበርበር፣ በታክስ ስወራና በተለያዩ ህገ ወጥ ድርጊቶች በግለሰቦች እጅ የገቡትን የመንግስት ሀብት ለማስመለስ እንዲሁም ከቅጣትና ከህገ ወጥ ንግድ ውርስ ገቢ ሊሆኑ የሚገባቸውን ገንዘቦች ገቢ ማስደረግን በተመለከተ በድርድር ብር ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ ተመላሽ መደረጉን ፤
በፍ/ቤት ውሳኔ፣ከወንጀል ቅጣትና ዋስትና ግዴታ ገቢ ከ3.8 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ መደረጉን፤
የመንግስትና የሕዝብ ጥቅም የሚነኩ የፍትሐብሄር ጉዳዮች ላይ ከክስ በፊት በድርድር ከ42 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ መደረጉን እና ክስ በመመስረት ከ71 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት መወሰኑን፤
በፍ/ቤት ክርክርና ክትትል በማድረግ ከ79 ሚሊዮን ብር በላይ መንግስት እንዳይከፍል ለማድረግ መቻሉን፤
በፍትሐብሔር የአፈጻጸም ክስ ከ142 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ መደረጉን፤ እንዲሁም
የተመዘበሩ የመንግስት ሀብትና ንብረት ከማስመለስ አንጻር በድርድር እና በአፈጻጸም ክስ 16.8 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ መደረጉ ሪፖርቱ አመለክቷል።
የፍትህ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሙሉቀን ታደሰ ሲያጠቃልል ቢሮው በ9 ወራት ውስጥ ጥሩ አፈፃፀም ማሳየቱን የገለጸ ሲሆን በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ አጽንኦት ሰጥተዋል ። ከእነዚህም ውስጥ በክልል ቢሮ ባለጸደቀ ውል መነሻ ክስ እንዳይከፈት፤ አዋጪ ያልሆነ መዝገብ ላይ ክስ መከፈት እንደሌለበት፤ በሀብት ማስመለስ አዋጅ መሠረት አደረጃጀት መፈጠር እንዳለበት፤ ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለብን፤ የፌደራል ጉዳዮች መዝገብ አያያዝ ከክልል መዝገቦች በተለየ ሁኔታ መደራጀት እንዳለበት እንዲሁም የ2019 የበጀት ዕቅድ እያንዳንዱ ዳይሬክቶሬት በፕሮግራም በጀትንግ መሠረት በማዘጋጀት በልማት ዕቅድ በኩል ለክልሉ ፋይናንስ እንዲሁም ፕላን ቢሮ መላክ እንዳለበት አቅጣጫ በማስቀመጥ በቀሪ የበጀት ዓመቱ ጊዜ ውስጥ የተለያዩ ክፍተቶችን በመሙላት አፈፃፀሙን ለማ
ሻሻል እንደሚሰራ አስታውቋል።





የኧሌ ዞን ፍትህ መምሪያ ህገ-ወጥ የሰዎች ፍልሰትና በሰዉ የመነገድ ተግባር ለመቆጣጠር የፍልሰት ትብብር ጥምረት አቋቁሟል
#ኮላንጎ:- መጋቢት 10/2018 ዓ/ም #(ኧዞመኮ_AZC)
የኧሌ ዞን ፍትህ መምሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል መከላከልና መቆጣጠር በወጣው አዋጅ ቁጥር 1178/2012 በማስፈጸሚያ ደንብ 4/2017 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠት የፍልሰት ትብብር ጥምረጥ አቋቁሟል፡፡
የኧሌ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጉድሳ ኩሲያ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ወጣቶች እና ሴቶች ለህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ተጋላጭና ለስደት ሰለባ ከመሆን መንግስት በሚፈጥረው የስራ ዕድል አማራጭ ሁሉ በመሰማራት በራስ ጥረት የመለወጥ አመለካከትን በማሳደግ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች ህገ-ወጥ የሰዎች ዝዉዉር ወንጀልን ለመከላከል ግንዛቤ በማያዝ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም በዛሬው እለትም ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመቅረፍና ዜጎች ለስራ ከሀገር ሀገር ሲንቀሳቀሱ ህጋዊ አሰራሮችን በማስቀመጥ የሚሄዱበትን ሀገር የሚሰሩትን ስራ አውቀው ስለሚሄዱበት ሀገርና ስለሚሰሩት ስራ በቂ ክህሎት ኖሯቸው ይንቀሳቀሱ ዘንድ አጋዥ የሚሆን የግንዛቤ ማስጨበጫ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በኧሌ ዞን በሰዉ መነገድና ሰዉን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ተከላካይ የትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባይነህ ግርማ በሰው የመነገድ ወንጀል አንዱ ሕጻናትን ከቦታ ቦታ በህገ-ወጥ መልኩ በማዘዋወር ለጉልበት ብዝበዛ፣ አካላዊና የስነልቦና ጥቃት መፈፀም በአዋጅ ቁጥር 1178/2012 በስፋት በመቀመጡ ህብረተሰቡ ወንጀልን በመከላከል ሂደት ዉስጥ ያለዉ ድርሻ በቁርጠኝነት ሊወጣ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
የዉይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በአዋጁ ላይ ያገኙት ግንዛቤ ህገ ወጥ የሰዎችን ዝውውር ወንጀል ተጋላጭነትን ለመከላከል እና አስፈላጊዉን ጥበቃ ለማድረግ የሚያስችል በመሆኑ ለህግ አካላት ተገቢዉን ትብብር እንደሚያደርጉ በመጥቀስ፤ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር በህይወት ላይ የሚያደርሰውን አስከፊነት በመረዳት ወጣቶች በተፈጠረው ህጋዊ አሰራር መሰረት ከዉጪ ሀገራት የስራ ስምምነት በተመቻቸው መንገድ ተጠቃሚ ለመሆን አጋዥ እንደሚሆኑ በውይይታቸው አስቀምጠዋል።
#መረጃው የኧሌ ዞን መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ነው !!


























