Home

Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!

Introduction

The Southern Ethiopia Regional Government has recently established the 12th regional state of the federation, and the executive bodies of the region have been reorganized under Proclamation No. 3/2015, Article 9/22/. One of the newly established sector offices is the Justice Bureau. The Bureau has been entrusted with the tasks and organization and procedures for youth from the region to the A service that meets the needs of the previous administrative levels of families, ensures the rule of law required in the center, and meets the needs of the community, which is efficient and accessible, and meets the needs of the service user community. In order to provide and satisfy the needs of the users, it is hoped that a consistent institutional arrangement will be developed and implemented from region to woreda by exchanging experiences with other peer regions, incorporating the experiences gained, and adapting them to the actual conditions of our region.

 

 

 

LATEST NEWS

የኧሌ ዞን ፍትህ መምሪያ ህገ-ወጥ የሰዎች ፍልሰትና በሰዉ የመነገድ ተግባር ለመቆጣጠር የፍልሰት ትብብር ጥምረት አቋቁሟል

የኧሌ ዞን ፍትህ መምሪያ ህገ-ወጥ የሰዎች ፍልሰትና በሰዉ የመነገድ ተግባር ለመቆጣጠር የፍልሰት ትብብር ጥምረት አቋቁሟል፦

 

#ኮላንጎ:- መጋቢት 10/2018 ዓ/ም #(ኧዞመኮ_AZC)

 

የኧሌ ዞን ፍትህ መምሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል መከላከልና መቆጣጠር በወጣው አዋጅ ቁጥር 1178/2012 በማስፈጸሚያ ደንብ 4/2017 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠት የፍልሰት ትብብር ጥምረጥ አቋቁሟል፡፡

 

የኧሌ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጉድሳ ኩሲያ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ወጣቶች እና ሴቶች ለህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ተጋላጭና ለስደት ሰለባ ከመሆን መንግስት በሚፈጥረው የስራ ዕድል አማራጭ ሁሉ በመሰማራት በራስ ጥረት የመለወጥ አመለካከትን በማሳደግ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች ህገ-ወጥ የሰዎች ዝዉዉር ወንጀልን ለመከላከል  ግንዛቤ በማያዝ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

 

ኃላፊው አክለውም በዛሬው እለትም ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመቅረፍና ዜጎች ለስራ ከሀገር ሀገር ሲንቀሳቀሱ ህጋዊ አሰራሮችን በማስቀመጥ የሚሄዱበትን  ሀገር የሚሰሩትን  ስራ አውቀው ስለሚሄዱበት ሀገርና ስለሚሰሩት  ስራ በቂ ክህሎት ኖሯቸው ይንቀሳቀሱ ዘንድ አጋዥ የሚሆን የግንዛቤ ማስጨበጫ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

 

በኧሌ ዞን በሰዉ መነገድና  ሰዉን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ተከላካይ የትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባይነህ ግርማ  በሰው የመነገድ ወንጀል አንዱ ሕጻናትን ከቦታ ቦታ በህገ-ወጥ መልኩ በማዘዋወር ለጉልበት ብዝበዛ፣ አካላዊና የስነልቦና ጥቃት መፈፀም በአዋጅ ቁጥር 1178/2012 በስፋት በመቀመጡ ህብረተሰቡ ወንጀልን በመከላከል ሂደት ዉስጥ ያለዉ ድርሻ በቁርጠኝነት ሊወጣ እንደሚገባ  ገልፀዋል፡፡

 

የዉይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በአዋጁ ላይ ያገኙት ግንዛቤ ህገ ወጥ የሰዎችን ዝውውር ወንጀል ተጋላጭነትን ለመከላከል እና አስፈላጊዉን ጥበቃ ለማድረግ  የሚያስችል በመሆኑ ለህግ አካላት ተገቢዉን ትብብር እንደሚያደርጉ በመጥቀስ፤ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር በህይወት ላይ የሚያደርሰውን  አስከፊነት በመረዳት  ወጣቶች በተፈጠረው ህጋዊ አሰራር መሰረት ከዉጪ ሀገራት የስራ ስምምነት በተመቻቸው መንገድ ተጠቃሚ ለመሆን አጋዥ እንደሚሆኑ በውይይታቸው አስቀምጠዋል።

 

#መረጃው የኧሌ ዞን መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ነው !!

wpChatIcon
wpChatIcon