Home

WELCOME TO THE SOUTH ETHIOPIA REGION STATE JUSTICE BUREAU

WE STAND TOGETHER FOR LAW,JUSTICE AND EQUITY!

Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!Thank you for reading this post, don't forget to subscribe!

Introduction

The Southern Ethiopia Regional Government has recently established the 12th regional state of the federation, and the executive bodies of the region have been reorganized under Proclamation No. 3/2015, Article 9/22/. One of the newly established sector offices is the Justice Bureau. The Bureau has been entrusted with the tasks and organization and procedures for youth from the region to the A service that meets the needs of the previous administrative levels of families, ensures the rule of law required in the center, and meets the needs of the community, which is efficient and accessible, and meets the needs of the service user community. In order to provide and satisfy the needs of the users, it is hoped that a consistent institutional arrangement will be developed and implemented from region to woreda by exchanging experiences with other peer regions, incorporating the experiences gained, and adapting them to the actual conditions of our region.

 

 

Latest News

“ምርጫው የዲሞክራሲ መገለጫ በመሆኑ፣ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የፍትህ አካላት የሕግ የበላይነትን የማስከበርና የዜጎችን መብት የማስጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው” ብለዋል አቶ ሙሉቀን ታደሰ

ወላይታ ሶዶ፣ ግንቦት 06/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ታደሰ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ “ምርጫ የዲሞክራሲ መገለጫ እንደመሆኑ፣ ይህ ሂደት በስኬት እንዲጠናቀቅ የፍትህ አካላት የሕግ የበላይነትን የማስከበርና የዜጎችን መብት የማስጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው” ብለዋል።

ምርጫ የሀገር መንግሥት ግንባታ ምሶሶ ከመሆኑ አንጻር የፍትህ ተቋማት ገለልተኝነት ወሣኝ ጉዳይ ብለዋል።

የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕረዚዳንት አቶ ምህረት ኩኬ እንዳብራሩት የምርጫ ሥነምግባር ለማስጠበቅ የፍትህ አካላት ገለልተኝነት ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል።

በምርጫ ወቅት ወንጀሎች ስከሰቱ የሰብአዊ መብት በማይጋፋ መንገድ እንዲሆን አሳስበዋል

የምርጫ ወንጀሎች በመለየት ፈጣን ፍትህ እንዲሰጥ ጊዚያዊ ችሎት መዘጋጀቱን አስረድተዋል

ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዲሆን የፍትህ ተቋማት ቁርጠኝነት ወሣኝ መሆኑን ገልጸዋል

የጸጥታ አካላት ገለልተኝነት ለምርጫው ውጤታማነት የጎላ ሚና እንደሚጫወት አስረድተዋል

ሠላማዊ ምርጫ ለማካሄድ ቅድሚያ ችግሩን በመለየት በመከላከል ላይ መሠረት በማድረግ ውጤታማነትን ለማስመዝገብ እንደሚሠራ ጠቁመዋል

የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጸጋው ስሞኦን እንደገለጹት የጸጥታ አካላት ገለልተኛ እንዲሆንና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ሥልጠናው ወሳኝ ጉዳይ መሆኑ የተገለጸው።

የምርጫ ቦርዶ አዋጅ መሠረት በማድረግ የጸጥታ አካላት ሕጉን በተከተለ መንገድ ተግበራዊ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

ፍትሕ ተቋማት ምርጫው በሕግ አግባብ እንዲያከናውኑ ሥልጠናው አቅም እንደሚፈጥር አስተያየታቸውን ገልጸዋል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ እና የወላይታ ዞን ፍትህ አካላት በጋር በመሆን ለሥር መዋቅር አካላት ማለትም ለቦዲቲ ከተማ፣ ለዳሞት ጋሌ፣ ለዳሞት ፑላሳ እና ለሻንቶ ከተማ ለተውጣጡ ዐቃቢያነ ሕጎች፣ ዳኞች፣ የፖሊስ አባላት እና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ያዘጋጁት የአቅም ግንባታ ስልጠና እና የምክክር መድረክ በቦዲቲ ከተማ በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

‎በመድረኩ 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ብቻ እንዲመራ፣ በምርጫ ሕጉ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎችንና የወንጀል ተጠያቂነትን በተመለከተ ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሯል።

7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና የላቀ እንደሆነ ተገለፀ።

‎ላስካ፡ ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም

‎የሠላም፣ የሰብዓዊ መብቶችና የዕድገት ማዕከል ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር በደቡብ ክልል ፍትህ ቢሮ አስተባባሪነት በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ የመራጮች ትምህርት ስልጠና ከተለያዩ ሲቪል ማህበራት ለተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ሰጥቷል።

‎ዜጎች በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ ስለሚኖራቸው ሚና፣ ኃላፊነቶች እና መብቶች እንዲሁም ለመምረጥ ብቁ ለሆኑ ዜጎች ስለምርጫ ሂደት፣ ሥርዓት፣ መሥፈርቶች እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ የሚፈጥሩ ርዕሶች ላይ ያተኮረ እንደሆነ በስልጠናው ተመልክቷል።

‎የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መርሆች ላይ ያተኮረ የስልጠና ሰነድ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የጠበቆች የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ሰነድ ማረጋገጫ ዳይሬክተር ዳይሬክቶረት አቶ ደስታ ዮሐንስ አቅርበው ውይይት ተደርጓል።

‎ዜጎች በምርጫ ሂደት ውስጥ በነፃነት የመምረጥና የመመረጥ አጠቃላይ መብቶች እንዲያውቁ፣ እንዲጠቀሙ፤ ምርጫን የሚመለከቱ የሕግ ማዕቀፎች ላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማስቻል ያለመ መሆኑን አቶ ደስታ ዮሐንስ ገልጸዋል።

‎በምርጫ ሂደት ውስጥ ባለድርሻ አካላት የሚኖራቸው ተሣትፎ እና ተግባራቸው እንዲሁም በምርጫ ተዓማኒነት፣ ግልፀኝነት እና የህዝብ ዓመኔታን በማረጋገጥ ረገድ ያላቸው አወንታዊ ተጽዕኖ የላቀ መሆኑን የባስኬቶ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚልክያስ ተሰማ ገልፀዋል።

‎መራጮች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም አካላዊ ሁኔታዎችን ጨምሮ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ላይ የተመሰረቱ የተለያዩ ፍላጎቶች ያላቸው እንደመሆኑ የምርጫውን ውጤታማነት በማረጋገጥ ረገድ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ባለድርሻ መሆናቸውን ተጠቁሟል።

የምርጫ ቦርድ መርሆዎችን በመከተል፣ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ፣ ከወገኝተኝነት በፀዳ መልኩ ባለድርሻ አካላት የዜግነት ኃላፊነትን በተገቢው እንዲወጡ በመድረኩ ጥሪ ቀርቧል።

በመጨረሻ 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የእግር ጉዞ በማድረግ መድረኩ ተጠቃሏል።

‎         ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም

‎              ላስካ